መዝሙር 519 በቀራንዮ ኮረብታ የዘፈን ግጥሞች
Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus. vertsion 2009
፩፡ በቀራንዮ ኮረብታ
ተሠዋልኝ ጌታ
ታላቅ ሥራ ፈጸመ
ሲኦልም ተረታ፤
የሰማይን በር የሚከፍት
ኢየሱስ ብቻ ነው፤
ሕያው የሆነው አዳኝ
መድኅኔ ዓለም ነው።
በዘላለማዊ ፍቅር
ላዳነኝ በጸጋ
ልወድስ ላመስግነው
ይህን የድል ጌታ።
በዘላለማዊ ፍቅር
ላዳነኝ በጸጋ
ልወድስ ላመስግነው
ይህን የድል ጌታ።
፪፡ ልስገድ ላመስግነው
ሞትን ላሸነፈው
ስለኔ ለተሠዋው
ደሙን ላፈሰሰው
በሥቃይ በችንካሩ
በመገረፍ ቁስሉ
ለኃጥዕ በደለኛ
ተከፈተ በሩ።
በዘላለማዊ ፍቅር . . .።
፫፡ እየመራኝ ሲወጣ
ከዓለም መከራ
የሕይወት አክሊል ስጭን
ከብፁዓን ጋራ፤
በአዲስ ስም ተጠርቼ
መቅረዜ እየበራ
ልኖር ነው በገነት ውስጥ
ከኢየሱስ ጋራ።
በዘላለማዊ ፍቅር . . .።