መዝሙር 470 በክንፉ ሥር የዘፈን ግጥሞች
Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus. vertsion 2009
፩፡ በክንፉ ሥር በሰላም እኖራለሁ
ጨለማው በዝቶ ፍርሃትም ቢያንቀኝ፤
እኔ አምነዋለሁ እንደሚጠብቀኝ፥
በርሱ ድኛለሁ እኔም ልጁ ነኝ።
ከርሱ ፍቅር ከርሱ ፍቅር፥
ማን ይችላል ሊለየኝ፥
በክንፉ ሥር ነፍሴ ታርፋለች፥
በሰላም ለዘላለም።
፪፡ በክንፉ ሥር ከኀዘኔ ስከለል
ልቤም ከናፍቆት ከሐሳብ ያርፋል።
ዓለም ደኅንነት ልትሰጠኝ አትችልም፥
ካንተ ግን ደስታ ሰላም ይገኛል።
ከርሱ ፍቅር . . .።
፫፡ በክንፉ ሥር ታላቅ ደስታ ይገኛል
ከዚያ ልሸሸግ ፈተናው እስኪያልፍ።
በአምላኬ ብርታት ጉዳት አይደፍረኝም፥
በኢየሱስ ጥላ በሰላም ልረፍ።
ከርሱ ፍቅር . . .።