መዝሙር 371 ክርስቶስ ኃጢአተኞችን በጸጋው ይቀበላል የዘፈን ግጥሞች
Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus. vertsion 2009
፩፡ ክርስቶስ ኃጢአተኞችን በጸጋው ይቀበላል
በላይኛውም መንገድ ሊመራቸው ይወዳል።
መዝሙሩን ዘምሩለት
በጸጋው ይቀበላል፤
መልእክቱን ግለጹለት፥
በጸጋው ይቀበላል።
፪፡ በጌታ ብንታመን ዕረፍትን ይሰጠናል
እኛን ኃጢአተኞችን የሱስ ይቀበለናል።
መዝሙሩን ዘምሩለት . . .።
፫፡ እርሱ አይኰንነኝም ወደርሱ ከቀረብሁኝ
በንጽሕና መንፈስ እርሱ ይጠብቀኛል።
መዝሙሩን ዘምሩለት . . .።
፬፡ የሱስ ኃጢአተኞችን በፍቅሩ ይቀበላል
እኔን እንኳን ከርሱ ጋር እንድኖር ያደርገኛል።
መዝሙሩን ዘምሩለት . . .።