መዝሙር 254 እዘምራለሁ ታሪኩን የዘፈን ግጥሞች
Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus. vertsion 2009
፩፡ እዘምራለሁ ታሪኩን
ለየሱስ ለሞተልኝ
ክብሩን ሁሉ እንደጣለ
በቀራንዮ መስቀል።
ልዘምር ያን ግሩም ታሪክ
ለየሱስ ለሞተልኝ
ዘምሩ ከቅዱሳን ጋር
በገነት ደጅ ባሕር ዳር።
፪፡ ጠፍቼ ነበር አገኘኝ
ስባክን እኔን ልጁን
አፍቃሪ በሆነው ክንዱ
ስቦ መራኝ መንገዱን።
ልዘምር . . .።
፫፡ ቆስዬ ነበር አዳነኝ
በድካምም ስማቅቅ
ብርሃን ሸሽቶ ፍርሃት ውጦኝ
ግን እርሱ ነፃ አወጣኝ።
ልዘምር . . .።
፬፡ የቀን ጨለማም ሲከብደኝ
በኃዘን ባሕር ስዋኝ
አዳኜ ከኔ ጋራ ነው
እጁም ለኔ መሪ ነው።
ልዘምር . . .።
፭፡ እስከ ሕይወት ወንዝ አድርሶኝ
ነፍሴን ያረካልኛል
ከዚያም በሰላም አሻግሮኝ
ምርጦቹን ያሳየኛል።
ልዘምር . . .።