መዝሙር 239 ቅዱስ ቅዱስ ቀዱስ እግዚአብሔር የዘፈን ግጥሞች
Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus. vertsion 2009
፩፡ ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ እግዚአብሔር
ስብሐት ላንተ በሰማይ ለምትኖር።
ይገባናል ምስጋናህን ልንዘምር፥
በልባችን ቅዱስ ቃልህ ይደር።
፪፡ ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ እግዚአብሔር
ነዋሪ አምላክ በሰማይ በምድር።
የምታቀል የኃጢአትን ቀንበር፥
በምሕረትህ ስጠን ሰላም ፍቅር።
፫፡ ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ እግዚአብሔር
ርኅሩኅ አምላክ በደልን የሚምር።
ስንለምንህ በኤድን ገነት ልንኖር፥
አካፍለነ ከብፁዓን ማኅበር።