መዝሙር 191 የኃጢአት ይቅርታ የዘፈን ግጥሞች
Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus. vertsion 2009
፩፡ የኃጢአት ይቅርታ
እንዴት ያለ ደስታ ነው።
ፍጹም ደስታ ይገኛል፥
የሕይወት ምንጭ ካለበት።
የሕይወት ምንጭ ካለበት
ዘላለማዊ ደስታ።
ፍቅር ሰላም ይገኛል፥
የሕይወት ምንጭ ካለበት።
፪፡ ከተሰቀለው ጌታ
ከእግሩ ሥር ወድቄ።
ለዘለዓለም ልኑር፥
የሕይወት ምንጭ ካለበት።
የሕይወት ምንጭ . . .።
፫፡ ይህ የጠለቀ ፍቅሩ
መንፈስን የሚያሞቅ።
ከላይ የወረደ ነው፥
የሕይወት ምንጭ ካለበት።
የሕይወት ምንጭ . . .።
፬፡ በችግር ማዕበል ላይ
በየሱስ እጅ ውስጥ መሆን።
ዕረፍትና ሰላም ነው፥
የሕይወት ምንጭ ካለበት።
የሕይወት ምንጭ . . .።
፭፡ ከማናቸውም ኃጢአት
ልቤ ፍጹም ነጽቶአል።
መዝሙሬን እዘምራለሁ፥
የሕይወት ምንጭ ካለበት።
የሕይወት ምንጭ . . .።