Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus vertion 1982
መዝሙር 277 ዓለት ቢፈርስም የዘፈን ግጥሞች
፩፡ ዓለት ቢፈርስም
ተራራ ቢወድቅም
እምነቴ እስከ ዘላለሙ ነው።
የኪዳኔም ጸጋ ከአንቺ አይርቅም
እንዲህ የሚልሽ መድኃኒትሽ ነው።
፪፡ ጌታ የሱስ ሆይ
ያን ቃል እንዳልረሳ
ተስፋህንም እንድታመን እርዳኝ።
ከመቃብሬም ከእንቅልፌ ስነሣ
ሕያው ቅዱስ ቃልህ ቤትህ ያግባኝ።