መዝሙር 495 ሞት ይገባን ነበር የዘፈን ግጥሞች
Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus. vertsion 2009
፩፡ ሞት ይገባን ነበር
የኃጢአት ደሞዝ ነውና
የዲያብሎስን ዕቅድ
በደሙ ያፈረሰው ጌታ ኢየሱስን፥
ልትገዛለትና ልታከብረው ይገባል
ይህን የድል ንጉሥ።
ልትገዛለትና ልታከብረው ይገባል
ይህን የድል ንጉሥ።
፪፡ የባሪያን መልክ ይዞ
ሁሉን ባዶ ያደረገው
የሰው ልጆች ፍቅር ግድ
ቢለው ነውና ውዱ አምላካችን፥
እርስ በርሳችን ልንዋደድ
ምሳሌ ሆነን የእግዚአብሔር ልጅ።
እርስ በርሳችን ልንዋደድ
ምሳሌ ሆነን የእግዚአብሔር ልጅ።
፫፡ እኛ በርሱ አምነን
ለዘላለም እንድኖር
አብ አንድያ ልጁን አዳኙን
መድኃኒት ጌታ የሱስን፥
ስለኔና ስላንተ እርግማን አደረገው
ይክበር ይመስገን።
ስለኔና ስላንተ እርግማን አደረገው
ይክበር ይመስገን።
፬፡ እኛ በርሱ ሆነን የእግዚአብሔር
ጽድቅ እንድንሆን
ኃጢአት ያላወቀውን ቅዱሱን
የእግዚአብሔር ልጅ ጌታ የሱስን
ስለኔና ስላንተ ኃጢአት አደረገው
ይክበር ይመስገን።
ስለኔና ስላንተ ኃጢአት አደረገው
ይክበር ይመስገን።