መዝሙር 93 አያለሁ የሱስ ዕርገትህን የዘፈን ግጥሞች
Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus. vertsion 2009
፩፡ አያለሁ የሱስ ዕርገትህን
ስታርግ ከምድራችን።
እኔ ግን እንደ እንግዳ
እኖራለሁ በምድር።
በኀዘን ድካም ውስጥ ነኝ
ገና ካባቴ ቤት ሩቅ ነኝ።
፪፡ ያን ክቡር አገር በእምነት
አሁንም ልመልከት።
ከኃጢአቴ ተፈትቼ
ልከብር በጌታዬ
ልኖር ከብፁዓን ጋራ
በሕያው አምላክ ከተማ።
፫፡ በሰማይ ቤት የለም ሌሊት
ጨለማ ኃዘን ጭንቀት
በዚያ አለ መዝገቤ
በዚያም ይሁን ልቤ።
ከየሱሴ ይኑረኝ ኅብረት
ጸጋ ይሰጠኝ ልኖርበት።
፬፡ ያረገው ወደ ላይ ከኛ
ይመለሳል ዳግመኛ።
እንዳይመጣ ሳናስበው
ተግተን እንጠብቀው።
እምነታችን እንዳይናጋ
ዘወትር በጸሎት እንትጋ።
፭፡ በቅዱስ ስምህ ያመነ
አንተን የተማጠነ።
መንግሥትህን እንደሚወርስ
ተስፋ ሰጠህ የሱስ ሆይ።
ብፅዕና ትሰጠዋለህ
በክብርም ታኖረዋለህ።