መዝሙር 84 አርነት ወጣሁኝ የዘፈን ግጥሞች
Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus. vertsion 2009
፩፡ አርነት ወጣሁኝ
በየሱሴ፤
ከጭንቄም አረፍሁኝ
በመድኃኒቴ።
የየሱስ ክርስቶስ ደም፥
ጥቅሙን ክብሩንም፥
ቀድሞ አላወቅሁም፥
አሁን ታይቶኛል።
፪፡ የጸጋው ምሥጢሩ
ተገለጠ፥
አምላክ በፍቅሩ
ልጁን ለወጠ።
ፍርድ ሲያስጨንቀኝ፥
ልቤም ሲያውከኝ፥
በርሱ ሰላም አለኝ
በመድኃኒቴ።
፫፡ ምን ያህል ደስታ
አለኝ አሁን?
ካምላኬ ይቅርታ
ምን ይበልጥ ይሆን?
ብዙ ቢጐድለኝም
አያስፈርድብኝም።
ፍርድ አይደርስብኝም
በመድኃኒቴ።
፬፡ እስከምሞት ልመን
በየሱስ ደም፥
ይምጣ የፍርድም ቀን
አያስፈራኝም።
በየሱስ ችሮታ፥
የሰማይ ደስታ፥
አለኝ አለኝታ
በመድኃኒቴ።