መዝሙር 81 የደስታ ዘመን ሆኖአል የዘፈን ግጥሞች
Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus. vertsion 2009
፩፡ የደስታ ዘመን ሆኖአል
ክርስቶስ ሞትን ድል ነሥቶአል።
ሲነሣም ከመቃብሩ
ተገለጠ ታላቅ ክብሩ።
፪፡ ከኵነኔ ሊያድነን
ተነሣ በሦስተኛው ቀን።
ከሞት ተነሥቶ አንደሚያርግ
በነቢያት ተነግሮአል።
፫፡ ቢጠብቁም መቃብሩን
ተነሣ ጥሶ ድንጋዩን።
የሕይወት ንጉሥም ቢሞት
አልቀረም በሲኦል ግዞት።
፬፡ ሲኦል አሁን ተሸነፈ
የስቃይ ዘመን አለፈ።
ጌታችን እንደ ተስፋው ቃል
ሃሌ ሉያ ተነሥቶአል።
፭፡ ከሞት ሥልጣን ያወጣኸን
ኦ የሱስ ክርስቶስ ተመስገን
ሙታን በሚነሡበት ቀን
የሕይወት ትንሣኤ ስጠን።