መዝሙር 72 ክርስቶስ ህያው ሆነ መቃብር በራ የዘፈን ግጥሞች
Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus. vertsion 2009
፩፡ ክርስቶስ ህያው ሆነ መቃብር በራ
መድኃኒት ተገኘ ትንቢትም ሞላ።
ግርማን ተጐናጽፎ ከሞት ተነሣ
ጠላት ተሸነፈ የሱስ ድል ነሣ።
የታተመው ድንጋይ ተፈነቀለ
ጠባቂዎቹም ደንግጠው ሸሹ
ሲኦልም ተሻረ ሃሌ ሉያ።
፪፡ ከጨለማ ጋራ ብርሃን ሲዋጋ
ብርሃን ለዘላለም ፍጹም ድል ነሣ።
ያ ሞት ተሸነፈ ድል ነሣ ሕይወት
ተስፋችን በረታ ለማጽናት እምነት።
እናንት ኀዘንተኞች ከልብ ዘምሩ
ከሞት አዳነነ በቸርነቱ
ሊኖር ከኛ ጋራ ሃሌ ሉያ።
፫፡ ሰማይና ምድር አሁን ታርቆአል
መቃብር የደስታ መንገድ ሆኖአል።
በመስቀል ትይዩ ያለቀሳችሁ
ሞት ተሸንፎአል ደስ ይበላችሁ።
ከዘላለም ሕይወት የጠፉት ሁሉ
ወደ ቸር እረኛ ይመለሳሉ
ሕይወት ያገኛሉ ሃሌ ሉያ።
፬፡ ቤተክርስቲያን ጸናች ነፍሳትም ይምጡ
በብርሃኑ ፍጥነት ሰፋ ትምህርቱ።
በዓለሙ ወጡ መልእክተኞቹ
ሞት እንኳ ሳይፈሩ ወንጌል ሊሰብኩ
ስለኛ ለሞተ ነጻ ላወጣን
ምስክር ሊሰጡ ሰውን ለማዳን
ደስታን ሊያበስሩ ሃሌ ሉያ።
፭፡ ለምን ታዝናላችሁ እናንተ ምእመናን
አጭር ነው ዘመኑ ሞት እስኪጠራን።
መሬት እንደ እናት ልታቅፋችሁ
እንደ ሕያው ዘር ግን ቶሎ ልትወጡ።
የዘራው ይመጣል ባጨዳ ጊዜ
እንክርዳዱን ሊለይ ከጥሩ ስንዴ
መከር ሊሰበስብ ሃሌ ሉያ።