መዝሙር 488 በመሐል ቤት ሆነህ የዘፈን ግጥሞች
Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus. vertsion 2009
፩፡ በመሐል ቤት ሆነህ
ዋለህ ከምትቀር
በራድ ወይም ትኩስ ብትሆን መልካም ነበር።
ለኔ የነበረህ ፍቅር በርዶብሃል፥
ካፌ ልተፋህ ነው ልጄ ልቤ አዝኖብሃል፥
ካፌ ልተፋህ ነው ንቃ
ልቤ አዝኖብሃል።
፪፡ በሥቃይ ጎዳና መስቀል ተሸክሜ
በክብር ላኖርህ ገዝቼህ በደሜ።
በትሣኤዬም ኃይል ሞትን አሸንፌ፥
ድል ያጎናጸፍኩህ ልጄ ጭንቅህን ገፍፌ
ምነው ጥለኸኝ ሄደክ እባክህ
ወጣህ ከእቅፌ።
፫፡ በመንፈስ ቅዱስ ኃይል
የጋለው ሕይወትህ
የፍቅር መግለጫ ምስክርነትህ።
እኔን ለማገልገል የነበረህ ስሜት፥
ከልብ የመነጨው ልጄ ትጋትና ጥረት
ምነው ቀዘቀዘ እባክህ
ያ ሁሉ ፍላጎት?
፬፡ የቀድሞ ኑሮህን ያንን ደስታ ጥለህ
ሥጋህ ተጎሳቍሎ ደህይተህ ቆርቁዘህ።
ጸጋዋ ተገፎ ነፍስህም ተራቁታ፥
እያየህ ስታዝን ልጄ ተርባ ተጠምታ፥
ምነው ዝም ትላለህ እባክህ
ስትቀር ተንገላታ?
፭፡ ለመኖር እንድችል ሆነህ ባለጸጋ
እንካ ወርቅ ውሰድ ያለ ምንም ዋጋ።
ለማየት እንድትችል ተኳል ዓይኖችህን
ደግሞም ለመሸፈን ልጄ እራቁትነትህን
እንካ ልብስ ውሰድ ፍጠን
በደሜ የነጻውን።