መዝሙር 457 የአምላክን ፍቅር የዘፈን ግጥሞች
Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus. vertsion 2009
፩፡ የአምላክን ፍቅር ለሰው ሁሉ አውራ
ከኃጢአትህ እንደመለሰህ፤
ዘወትርም ላንተ እንደሚያስብልህ፥
ባለህበት ዙሪያ አብራ።
ባለህበት ዙሪያ አብራ፥
ባለህበት ዙሪያ አብራ።
ከእግዚአብሔር የራቀውን ሰው
እንድትመልሰው፥
ባለህበት ዙሪያ አብራ።
፪፡ ክርስቶስ አንተን ከባርነት ቀንበር ሊያወጣህ
ከሰማይ ሰማያት ወረደ፤
በመስቀል ላይ ላንተ ሲልም እንደሞተልህ፥
ባለህበት ዙሪያ አብራ።
ባለህበት . . .።
፫፡ የአምላክን ውለታ ለሰው ሁሉ ንገር
ነፍስህን ከሞት እንዳዳናት፤
በኃጢአተኛ መመለስ እንደሚደሰት፥
ባለህበት ዙሪያ አብራ።
ባለህበት . . .።