መዝሙር 430 እንግዳ ስደተኛም አንዳባቶቼ ነኝ የዘፈን ግጥሞች
Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus. vertsion 2009
፩፡ እንግዳ ስደተኛም አንዳባቶቼ ነኝ
ቤቴም በላይ ነው እንጂ
በዚህ ዓለም አይገኝ።
በላይ ግን ቸር አባቴ
ቤቱን ከፍቶልኛል፥
እኔም ከእርሱ ጋር
መኖር ያስመኘኛል።
ግሩም ግሩም ነው ተስፋዬ
ወዲያ ስመለከት ይግላል ደስታዬ።
፪፡ ስለኔ ሞትን ቀምሶ
ከሞትም ያዳነኝ፥
ቸር ወዳጄን የሱስን በዚያ ልገናኝ ነኝ።
አስደሳች ነገር ሁሉ
በምድር ባገኘም፥
ወዲያ ግን ወደርሱ
ናፍቆት አይለቀኝም።
ግሩም ግሩም ነው . . .።
፫፡ ኃጢአት በምድር ላይ
ሁሉን አረከሰ፥
እንደ ውኃ ሙላትም
ሁሉን አዳረሰ።
ባያስፈርድብኝ እንኳ
ሰላም ይነሣኛል
ወዲያ ግን ስገባ ፍጹም ይለቀኛል።
ግሩም ግሩም ነው . . .።
፬፡ ልቆይ ልታገስ ገና
አይቀርም ተስፋዬ፥
ሊወስደኝ ወደ እርሱ
ይመጣል ጌታዬ።
አሁን በእምነት ብቻ
ያለኝን ንብረቴን፥
ያወርሰኛል በሙሉ ስደርስ ወዳገሬ።
ግሩም ግሩም ነው . . .።