መዝሙር 28 ስሙ መላእክት ሲዘምሩ የዘፈን ግጥሞች
Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus. vertsion 2009
፩፡ ስሙ መላእክት ሲዘምሩ
ክብር ለአምላክ እያሉ
ሰላም ይሁን በምድር ላይ
አምላክ ሰውን ታርቆአል።
ደስ ይበላችሁ ዘምሩ
ድል ተገኘ እልል በሉ
መልእክቱን አስተጋቡ።
ክርስቶስ የሱስ ተወልዶአል
ስሙ መላእክት ሲያውጁ
ክብር ለአምላክ እያሉ።
፪፡ ክርስቶስ የክብር ንጉሥ
ዘለዓለማዊ አምላክ
ከሰማያት ወረደ
ከድንግል ተወለደ
አምላክ ሥጋ ለበሰ
ሰው ሆኖ ተገለጠ
ከእኛም ጋር ተዛመደ
ክርስቶስ የኛ አማኑኤል
ስሙ መልአክት ሲያውጁ
ክብር ለአምላክ እያሉ።
፫፡ ምስጋና ለሰላም ንጉሥ
በጽድቅ ፀሐይ ለሚነግሥ
ብርሃን ሕይወትን አመጣ።
በማዳን ኃይል ተነሣ
ክብሩን ለሰው ልጅ ሠዋ
ሞትን ሻረ በድንቅ ሥራ።
በመምጣቱ ሰው ዳነ
ዳግም ሕይወት ተገኘ።
ስሙ መላእክት ሲያውጁ
ክብር ለአምላክ እያሉ።