መዝሙር 269 አምላክ በምሕረቱ ብዛት የዘፈን ግጥሞች
Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus. vertsion 2009
፩፡ አምላክ በምሕረቱ ብዛት
ለሕይወት መረጠነ
በየሱስ ክርስቶስ ቅዱስ ደም
ከኃጢአት አጠበነ።
ትምክህታችንን አስቀረ
ዕዳችንንም ከፈለ
በጸጋው ይቅር አለን።
፪፡ የአምላክ ትእዛዝ ቅዱስ ነው
መታዘዝ ግን አቃተን
አዳም ከበለስ ፍሬ በልቶ
ሁላችንን አሳተን።
ከርሱ የምንወለድም
ያምላክን ሕግ ፈቃዱንም
መፈጸሙን አልቻልንም።
፫፡ ሕግ ሁሉ ግን እስኪፈጸም
ከፍርዱ አናመልጥም
የወልድን ጽድቅ ካልለበስን
ሕይወትን እናገኝም።
ጌታ ሆይ እናመስግንህ
ከዘለዓለም ኩነኔ
በልጅህ ስላዳንከን።
፬፡ ያለምን ሁሉ ኃጢአት
ሲሸከም የመጣልን
ያምላክ ልጅ በመስቀል ሲሞት
ኦሪትን ፈጸመልን።
መድኃኒታችን የሠራውን
በእምነት ብንቀበለው
ሕጉ አይፈርድብንም።