መዝሙር 218 ምድራዊቱ ሕይወቴ ስታልፍ የዘፈን ግጥሞች
Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus. vertsion 2009
፩፡ ምድራዊቱ ሕይወቴ ስታልፍ
እሄዳለሁ፥
አምላክ ወዳዘጋጀልኝ ቤት
እሄዳለሁ።
እሄዳለሄ በክብር
እሄዳለሁ፥
ሃሌ ሉያ እያልኩ እየዘመርኩ
እሄዳለሁ።
፪፡ የዓለምን ጨለማ ትቼ
እሄዳለሁ፥
ታሥራ እንደ ተለቀቀች ወፍ
እበራለሁ።
እሄዳለሁ . . .።
፫፡ የችግር ጊዜ ሁሉ አልፎ
እሄዳለሁ፥
ዘላለም ደስታ ወዳለበት፥
እሄዳለሁ።
እሄዳለሁ . . .።