መዝሙር 199 የሱስ ሆይ ባንተ ያመነ የዘፈን ግጥሞች
Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus. vertsion 2009
፩፡ የሱስ ሆይ ባንተ ያመነ
በእውነት እርሱ ብፁዕ ሆነ።
ቤዛውም አንተ ሁነሃል
ስላንተም አብ ይወደዋል።
፪፡ ነፍሴ ከሞት እንድትድን
አፈሰስህልኝ ደምህን።
ሕይወትህን ለውጥህልኝ
ባምላኬም ፊት አጸደቅኸኝ።
፫፡ ሕያው መሥዋዕት ሁነህልኝ
ከክፉ መቅሰፍት አዳንኸኝ።
ዕዳዬንም ከፈልህልኝ፤
በሕይወትህ ጽድቅ ሰጠኸኝ።
፬፡ በሞትህ ኦ መድኃኒቴ
ሕግን ፈጸምኸው ስለኔ።
የሱስ ሆይ ባንተ ካመንሁ
ፍጹም ጻድቅ እሆናለሁ።
፭፡ የአምላክ ልጅ ያደረግኸኝ
አንተ ወደ አብ አቅርበኝ።
ከምድርም በሞት ስለይ
ርስቴን ከሰማይ አውርሰኝ።
፮፡ ግን ጌታ ሆይ ደካማ ነኝ
በጸጋህ ኃይል አጠንክረኝ።
ሰይጣን እንዳያሸንፈኝ
ሁልጊዜ አንተ ጠብቀኝ።
፯፡ የጀመርህልኝን ሥራ
እስከ ፍጻሜውም ሥራ።
ዘወትር በመንፈስህ ምራኝ
ወደ ሰማይም አድርሰኝ።