መዝሙር 162 ያልደረስሁበት አክሊል አለኝ የዘፈን ግጥሞች
Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus. vertsion 2009
፩፡ ያልደረስሁበት አክሊል አለኝ
አምላኬ ሆይ፥ አሳስበኝ።
ዓለምም እንዳያታልለኝ፥
ስታክት ና ኃይል ስጠኝ።
፪፡ ያልደረስሁበት ርስትም አለኝ
እንድወርሰው ጌታ እርዳኝ።
በወጥመዱም እንዳያጠምደኝ
ከሰይጣን ተንኰል ጠብቀኝ።
፫፡ ጌታዬ ሆይ ና የሞትህልኝ
በቅዱስ እጅህ ደግፈኝ።
ወደ ሰማይ ቤት ስታደርሰኝ
ያን ቅዱስ አክሊሌን ስጠኝ።