መዝሙር 1 ለእስራኤል አምላክ የዘፈን ግጥሞች
Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus. vertsion 2009
፩፡ ለእስራኤል አምላክ
ምስጋና፥ ክብር እንስጠው።
ስለ ታላቅ ሥራው፥
ለዘላለም ይባረክ።
ሕዝቡን ጎብኝቶአል፤
የመድኃኒትም ቀንድ
እርሱ አስነሣልን፤
በንጉሥ ዳዊት ቤት።
፪፡ ከጥንቱ ጀምሮ
ለነበሩት ብፁአን፤
በነቢያቱ አፍ
እንደ ተነገረልን፥
ከጠላቶቻችን
ፍጹም አድኖናል።
ምሕረቱንም ሰጠን
በጸጋው ትሩፋት።
፫፡ ካባቶቻችን ጋር
ያደረገውን ኪዳን፥
የሰጠንን ተስፋ
መሐላውን አጸና።
ለአብርሃም ያለውን
ሰጥቶናል መዳንን፤
ፍጹም አድኖናል
ከጠላቶቻችን።
፬፡ አሁን ያለ ፍርሃት
በእውነት በቅንነት፤
በፊቱ ሁሉ ቀን
እርሱንም እናገልግል።
አንተ ሕፃንም ሆይ፥
የልዑል ነቢይ ነህ፤
መንገዱን ትጠርግ ዘንድ፥
ቀድመህ ትሄዳለህ።
፭፡ እ-ግ-ሮ-ቻ-ች-ንን
በቅን መንገድ ሊመራ፥
እኛንም ባሰበን፥
ብርሃንም ባወጣልን፥
በአምላክ ምሕረት
ለኃጢአት ስርየት
የደኅነንት እውቀት
ለኛ ትሰጣለህ።