Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus vertion 1982
መዝሙር 98 የሱስ ኃጢአቴን ወስዶ የዘፈን ግጥሞች
፩፡ የሱስ ኃጢአቴን ወስዶ
በመስቀል ላይ ሞተልኝ።
ከፍርድም ከኵነኔም
አርነት አወጣኝ።
ለየሱስ ችግሬን ሁሉ
አሁን አስታውቃለሁ።
በክቡር ደሙ ብቻ
ኃጢአቴን ያጠፋል።
፪፡ ጭንቀቴን ሁሉ ለእርሱ
አሁን እነግረዋለሁ።
በታላቅ ቸርነቱ
ረድኤት ይሆነኛል።
ከችግርና ከድካም
እረፍት ይሰጠኛል
እርሱም በጥልቅ ኀዘኔ
ጽናት ይሆነኛል።
፫፡ ተስፋዬን በየሱስ
ፍጹም አድርጌአለሁ።
በቀኝ እጁ ሲይዘኝ
አንዳችም አልፈራም
ያ ድንቅ ስም የሱስ ክስርቶስ
ልዑል አማኑኤል።
ለነፍሴ መጽናናት
ሲሆን ይበቃኛል።
፬፡ እኔ የሱስን ልምሰል
በትሕትና ገርነት።
እንደ የሱስም ልሁን
በሕይወቴ ሁሉ።
ዕለተ ሞቴ ሲደርስ
ወደ አእላፋት
ብፁዓን እሄዳለሁ
ልኖር በአንድነት።