Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus vertion 1982
መዝሙር 71 ክርስቶስ የእኛ መመኪያ የዘፈን ግጥሞች
፩፡ ክርስቶስ የእኛ መመኪያ
በመስቀል ተሰቅሎልናል
ነፍሳችንን ለማውጣት ሲል
ወረደልን ወደ ሲኦል።
በታላቅ ግርማ ሲነሣ
ድል የእኛ ሆኖልናል።
፪፡ ምስጋና ይሁነው ለአብ
ስለ ላከልን የሱስን
መድኃኒት እንዲሆንልን
ከሞት ፍርድ እንዲያድነን።
ስለኛ የተሠዋው በግ
በከበረ ደሙ ገዛን።
፫፡ ባንተ መከራና ሥቃይ
ተከፈተ የሰማይ ቤት
እኛም እንናፍቃለን
መጥተን ክብርህን ልናይ።
ከሥጋ ምኞት ጠብቀን
ከሚሆን የመንፈስ ሥቃይ።
፬፡ አማላጅ አለን ከአብ ዘንድ
የሚያስተሰርይ ኃጢአት
እርሱም ኢየሱስ ክርስቶስ ነው
የኛ ሊቀ ካህናት።
በሙሉ እምነት እንቅረብ
ወደ ኃያል አምላካችን።
፭፡ ወንጌል የሚለው ጽደቄ ነው
ሳልጠራጠር አምናለሁ
የሱስም የዓለም ቤዛ
ሆኖ መምጣቱን አውቃለሁ።
ቅዱስ ቃሉ መሪ ሁኖኝ
በሰማይ ቤት እገባለሁ።