መዝሙር 507 ጠላቶቼን እንድወድ ጌታ የዘፈን ግጥሞች
Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus. vertsion 2009
፩፡ ጠላቶቼን እንድወድ ጌታ አስተማረኝ
በመስቀል ተቸንክሮ ፍቅሩን ገለጠልኝ።
መልካም ፍቅር ኦ! መልካም ፍቅር
ተወለደ በበረት ለኛ ለመሰቀል ለመሰቀል
ያዳምን ልጆች ኃጢአት በደሙ ለመክፈል
ያዳምን ልጆች ኃጢአት በደሙ ለመክፈል።
፪፡ መድኅኔ አስተምሮኛል በፍቅሩ እንድመራ
ያዘነን እንዳጽናና ላጣው እንድራራ።
ይገባኛል ኦ! ልታዘዘው እርሱ የኔን መከራ
ችሎ ሞቶአልና ሞቶአልና
ይገባኛል እኔም ልጓዝ በርሱ ጎዳና
ይገባኛል እኔም ልጓዝ በርሱ ጎዳና።
፫፡ በምድር የምናያቸው ሁሉም ይጠፋሉ
እምነት ተስፋና ፍቅር ጸንተው ይኖራሉ።
ጌታ ያዛል እንድንዋደድ
እርሱ ነፍሱን ለኛ እስኪሰጥ አፍቅሮናል
አፍቅሮናል
እርስ በርሳችን ልንዋደድ ይገባናል
እርስ በርሳችን ልንዋደድ ይገባናል።
፬፡ ምስጋና ይገባሃል ክቡር መድኃኒቴ
በሰማያዊ ፍቅር ዳበረ ሕይወቴ።
ሃሌ ሉያ ኦ! ለጌታዬ
በለመለመ መስክ ኢየሱስ ይመራኛል
ይመራኛል
በየለቱ የጌታ ፍቅር ይታየኛል
በየለቱ የጌታ ፍቅር ይታየኛል።