መዝሙር 243 አምላክን አክብሩ የዘፈን ግጥሞች
Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus. vertsion 2009
፩፡ አምላክን አክብሩ
እሙን ነው ምክሩ
ይስፋ ክብሩ።
በኃይሉ ነግሦአል።
ጸጋን ለግሦናል
እንዴት ያስደንቃል
ታላቅ ፍቅሩ።
፪፡ ተዋረደ ለሰው
ጽዋውም መረረው
ሲቀበለው።
አዳኛችን ሲሞት
መላእክት አደነቁ
መስቀሉ ሕይወት
ሊሰጠን ነው።
፫፡ ምሕረቱ ታላቅ ነው
ሊያመሰግነው
አይበቃም ሰው።
አንድ ቀን ግን በሰማይ
ግርማውን በግልጥ ስናይ
ምስጋናው እንደ ባሕር
ያስተጋባል።