መዝሙር 161 አምላክ ከእናንተ ዘንድ ይሁን የዘፈን ግጥሞች
Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus. vertsion 2009
፩፡ አምላክ ከእናንተ ዘንድ ይሁን።
ዘወትር በቃሉ ይምራችሁ፥
በፍቅሩ ይሸከማችሁ፥
እስክንገናኝ በየሱስ ፊት።
በሰማይ በሰማይ፥
በሰማይ እስክንገናኝ፥
በሰማይ በሰማይ፥
እስክንገናኝ በየሱስ ፊት።
፪፡ አምላክ ከእናንተ ዘንድ ይሁን።
ከጉዳት ይጠብቃችሁ፥
መናን ከሰማይ ይስጣችሁ፥
እስክንገናኝ በየሱስ ፊት።
በሰማይ . . .።
፫፡ አምላክ ከእናንተ ዘንድ ይሁን።
ፈተና ሲያስፈራችሁ፥
በኃይሉ ያጠንክራችሁ፥
እስክንገናኝ በየሱስ ፊት።
በሰማይ . . .።
፬፡ አምላክ ከእናንተ ዘንድ ይሁን።
አትካዱ ዓላማችሁን፥
ሞት እንኳ ቢሆን አትፍሩ፥
እስክንገናኝ በየሱስ ፊት።
በሰማይ . . .።