መዝሙር 105 ክብር ሁሉ ላንተ ይሁን የዘፈን ግጥሞች
Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus. vertsion 2009
፩፡ ክብር ሁሉ ላንተ ይሁን
ዘላለማዊው አምላክ ሆይ
ጸጋን እውነትን ተሞልተህ።
ወደ እኛ ለቀረብከው
ደኅንነትን ለኛ ሰጠህ።
በምድር ሰላም አስገኘህ
ሥሉስ አምላክ ተመስገን።
፪፡ ምስጋና ክብር እንስጥህ
እግዚአብሔር አብ አምላካችን።
ፍርድህ ሁሉ በቅንነት
በጥበብም የተሞላ
ፍጹም ዘላለማዊም ነው።
ፈቃድህ በኛ ላይ ይንገሥ
ለኛ በጎ ነውና።
፫፡ ጌታ ኢየሱስ የኛ አምላክ
የቅዱስ እግዚአብሔር ልጅ።
ሰላምህን የሰጠኸን
የባዘንነውን የፈለግኸን
ክቡር የእግዚአብሔር በግ።
ጩኸታችንን አደመጥክ
ምሕረትህንም ሰጠኸን።
፬፡ አምላካችን መንፈስ ቅዱስ
ምስጋና ክብር ይገባሃል።
ዕረፍትን የምትሰጠን
ጠባቂያችን የማትተውን።
ጭንቃችንን ከኛ አራቅህ
አጽናኛችንም አንተ ነህ
አምነን እናመልክሃለን።