መዝሙር 87 ከልባችሁ በአፋችሁ የዘፈን ግጥሞች
Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus. vertsion 2009
፩፡ ከልባችሁ በአፋችሁ
ክርስቶስን አመስግኑ።
በመቃብር ሦስት ቀን ተኛ
እንዲድን ዓለም ሁሉ።
ከመቃብሩ በግርማ
ተነሣ ሃሌ ሉያ።
፪፡ የኛን ሥራ እርሱ ሠራ
ለኛ ጽድቅን ሊሰጠን።
ኃጢአታችን ጭንቀታችን
አሁን ፍጹም ጠፍቶአል።
በሞት ፈንታ ሕይወት ደስታ
ሰጥቶናል ሃሌ ሉያ።
፫፡ ክርስቶስ ሊያድነን መጣ
ያለም ቤዛ እርሱ ነው።
አሁን ሰይጣን ኃይሉን አጣ
ሥልጣን ሁሉ የወልድ ነው።
እኛን ኃጢአተኞችን
አዳነን ሃሌ ሉያ።
፬፡ እናንተ ምእመናን ሁሉ
አምላክን አመስግኑ።
አንድያ ልጁን አክብሩ
ስለ ታላቅ ምሕረቱ።
ለሚቀድስ መንፈስ ቅዱስ
ዘምሩ ሃሌ ሉያ።