መዝሙር 70 የአምላክ ልጅ ይህ ቸር የዘፈን ግጥሞች
Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus. vertsion 2009
፩፡ የአምላክ ልጅ ይህ ቸር የፍቅር ጌታ
በበረት ውስጥ ስለኔ ተወለደ
በቤተ ልሔም ስለኔ ተንገላታ
ፍጥረት ሁሉ ለርሱ ያቅርብ ምስጋና።
ችግርን የሚያውቅ ይህ የሕማም ሰው
ውስጣዊ ልቤን እንዴት ዳሰሰው።
ተንቆ ቢኖር በሰው ተጠልቶ
አልተመለሰም ሥራውን ትቶ።
፪፡ እንደ ጠቦት በሸላቾች ፊት ዝም አለ
ሸክማችንን መድኃኒታችን ቻለ።
አፉን ሳይከፍት በጠላት ፊት ዝም አለ
ፍቅርን ለብሶ መስቀሉን ተሸከመ።
ጐልጐታ ወጣ ሲድህ ሲቧጥጥ
ምድር ሲፍቀው ገላውን ሲልጥ።
የኅዘን ቀን ነው ሆኖም የደስታ
እርሱ ተረግጦ እኛን ሲፈታ።
፫፡ ዓለም በታላቅ ፍርሃት ተጨነቀ
ነፍሱን ሰጠ ያ ቅዱስ የአምላክ በግ።
ኃይል ወጣና ከዓለም ንጉሥ ሥቃይ።
ከኃጢአት ፈጽሞ እኔን ሊያድን።
ከነፍሱ ድካም ፍሬን ያያል
ኋላም ዋጋውን ዘሩንም ያጭዳል።
ይህ ጻድቅ ጌታ እኔን አጽድቆ
እድሜው ይረዝማል ይኖራል ከብሮ።