መዝሙር 65 ከየሱስ ጐን የፈሰሰውን የዘፈን ግጥሞች
Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus. vertsion 2009
፩፡ ከየሱስ ጐን የፈሰሰውን
ቅዱስ ደሙን አውቃለሁ።
በዚህም ደም ከኃጢአቴ
ከበደል ነጽቻለሁ።
ጽድቅና ሕይወት ክርስቶስ ነው።
በደሙ ገዛ ሁሉን ሰው።
በደም፥ በደም፥ በክርስቶስ ቅዱስ ደም።
፪፡ በእምነት የምመለከተው
አንድ ድንቅ መስቀል አውቃለሁ።
ወደዚህ መስቀል በተስፋ
ዓይኖቼን አነሣለሁ።
በዚህ በእንጨት መስቀል ላይ
ተቀብሎ የሞት ሥቃይ
ከሞት ከሞት ክርስቶስ አድኖኛል።
፫፡ ወደ ምድር የወረደውን
አንድ ቸር ወዳጅ አውቃለሁ
ይህም ወዳጅ የአምላክ ልጅ
መሆኑን አምኛለሁ።
ኃጢአተኛውን ለማዳን
ሽሮአል የሞትን ሥልጣን፤
ለኔ፥ ለኔ፥ ስለኔ ሞቶአል።
፬፡ ደስታ ከቶ የማያልቅበት
አንድ ቅዱስ ቤት አውቃለሁ፤
በአዲስ ኢየሩሳሌም
ብፅዕናን አገኛለሁ።
ለገዛኝ መድኃኒቴ
እዘምራለሁ ውዳሴ፥
በቤት፥ በቤት፥ በሰማያዊ ቤት።