መዝሙር 567 በራቀው ኮረብታ (አሮጌ መስቀል) የዘፈን ግጥሞች
Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus. vertsion 2009
፩፡ በራቀው ኮረብታ
አንድ አሮጌ መስቀል
ቆሟል ለብሶ የጭንቅ ኃፍረት።
እኔ እወደዋለሁ
ያን አሮጌ መስቀል
ያለም መሥዋዕት ስለሞተበት።
ልምረጠው ያን አሮጌ መስቀል
የጦርነት ጊዜዬም እስኪያልፍ
አልክድም ያን አሮጌ መስቀል
አንድ ቀንም በላይ ዘውዴ ነው።
፪፡ ያን አሮጌ መስቀል
የተናቀው ባለም
ፈጥሯል በኔ ታላቅ መገረም
ውዱ የአምላክ በግ
ለቀራንዮ መስቀል
ክብሩን ንቆ መጥቶልኛል።
ልምረጠው . . .።
፫፡ በዚያ አሮጌ መስቀል
በደሙም መታጠብ
ያሳየኛል ግሩም እምነት
በዚያ መስቀል ላይ ነው
የሱሴ የሞተው
ሊያፈስልኝ ለኔ ምሕረት።
ልምረጠው . . .።
፬፡ ለዚያ አሮጌ መስቀል
ታማኝ እሆናለሁ
ኃፍረቱንም እችላለሁ።
አንድ ቀን ይጠራኛል
ወደ ራቀው ቤቴ
ሊያወር-ሰኝ ክብሩን ውድ አባቴ።
ልምረጠው . . .።
(ይህ መዝሙር በተለየ ትርጓሜ መዝሙር 62 ላይ ይገኛል።)