መዝሙር 56 ያምላክ ልጅ በመስቀል ላይ የዘፈን ግጥሞች
Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus. vertsion 2009
፩፡ ያምላክ ልጅ በመስቀል ላይ
የተቀበለው ሥቃይ፥
ሕይወትን ሊሰጠኝ ነው
በእምነት ስቀበለው።
፪፡ በመስቀል ያፈሰሰው፥
ንጹሕ ቅዱስ ደሙን ነው።
ከክፋቴም አጠበኝ፥
ባምላክ ፊት አጸደቀኝ።
፫፡ ወንበዴው የጸለየው
ለእኔም ጸሎቴ ነው
በመንግሥትህ አስበኝ
ጌታዬ ተለመነኝ።
፬፡ የሱስ ሆይ በፈቃድህ፥
በመስቀል ተሰቀልህ።
እኔ ካምላክ እንዳልጣል፥
ግሩም ተስፋ ሰጥተኸኛል።
፭፡ አብ ሆነልኝ አባቴ፥
እኔም በመድኃኒቴ
የሚወደኝ ልጁ ነኝ፥
በእቅፉም ተቀበለኝ።