መዝሙር 530 የሱስ በመስቀል የሞተው የዘፈን ግጥሞች
Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus. vertsion 2009
፩፡ የሱስ በመስቀል የሞተው፥
እኛ እንድንድን ነው።
በምነት ወደ ተሰቀለው
ብንጠጋ፥
ብፁዓን ነን ባምላክ ጸጋ።
፪፡ እባሕር የተጣለ ፍም፥
ፍጹም እንደሚጠፋ፥
እንዲሁም ያለም ኃጢአት
ኦ ተአምራት
በቅዱስ ደሙ ጠፋ።
፫፡ ምእመናን የምሥራቹን
እንቀበል በደስታ።
በጽድቁ ስለ ሸፈነን፥
አጸደቀን
ከኃጢአታችን ሁሉ።
፬፡ ሰይጣን በጣም ቢፈትነን፥
ቢያታልለን እንኳን፥
የሱስ ዘወትር ይረዳናል።
ያደርሰናል
ወደ ዘላለም ደስታ።