መዝሙር 52 ኑ ሁላችን እንመልከት የዘፈን ግጥሞች
Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus. vertsion 2009
፩፡ ኑ ሁላችን እንመልከት
የጌታችንን ሥቃይ
ኃጢአትን ሊያስወግድ
ተሰቅሎ በመስቀል ላይ።
በየሱስ ክርስቶስ ሕማም
ተገኝቶልናል ሰላም።
፪፡ የየሱስ እጅና እግር
ተቸንክሮ ይታያል
የእሾህ ዘውድ ተደፍቶበት
ግንባሩን አቁስሎታል።
በየሱስ ክርስቶስ ሕማም
ተገኝቶልናል ሰላም።
፫፡ ነፍሴን በእጅህ ተቀበል
ሲል አባቱን ለመነ።
በመጨረሻም በመስቀል
ራሱን አዘነበለ።
በየሱስ ክርስቶስ ሕማም
ተገኝቶልናል ሰላም።
፬፡ ሰው ሆይ ስለ ኃጢአትህ
የሱስ ክርስቶስ ሞቶአል።
በደልህ እስከ መስቀል ሞት
መድኅኑን አድርሶታል።
በየሱስ ክርስቶስ ሕማም
ተገኝቶልናል ሰላም።