መዝሙር 499 የኢየሱስን መልካሙን ድምፅ የዘፈን ግጥሞች
Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus. vertsion 2009
፩፡ የኢየሱስን መልካሙን ድምፅ
ሰምተሃል ወይ ወንድሜ ሆይ?
ሁሉን ትተህ ተከተለኝ፥
አገልጋዬ ሁነኝ ይልሃል።
አምላኬ ሆይ፥ ልከተልህ፥
አምላኬ ሆይ፥ልከተልህ፥
አምላኬ ሆይ፥ ወድጃለሁ፥
ልከተልህ መላውን ዘመኔ።
፪፡ ትችላለህ ወይ ልትጠጣ
የጌቴሴማኒን ጽዋ?
ለጸሎት ትነቃለህ ወይ?
አባትህን ልትለምነው?
አምላኬ ሆይ . . .።
፫፡ የወጣትነትህ ኃይል
ልትሰጥ ትወዳለህ ወይ?
ትሰጣለህ ወይ ሕይወትህን?
ለጌታ ለየሱስ መድኀንህ።
አምላኬ ሆይ . . .።
፬፡ እንግዲህ ወንድሜ ሆይ፥ ና
እምነትህን የጠበቅኸው፤
አምላክህ ወዶአልና፥
የሕይወትን አክሊል ሊሰጥህ።
አምላኬ ሆይ . . .።