መዝሙር 489 በጽዮን ደንጊያ አኖረ የዘፈን ግጥሞች
Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus. vertsion 2009
፩፡ በጽዮን ደንጊያ አኖረ
ልዑል እግዚአብሔር፤
በእርሱ ዘንድ የከበረ፥
የተናቀ በምድር።
፪፡ የማዕዘኑም ራስ የሱስ ነው
የሚያምንበት፤
ከቶ አያፍርም አይወድቅም፥
ግን ያገኛል ሕይወት።
፫፡ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው
ይህም የማዕዘን ራስ፤
ጽኑ መሠረት እርሱ ነው፥
ዘላለም የማይፈርስ።
፬፡ ያለርሱ መሠረት የለም
ሰው የሚጸናበት፤
በራሱ ኃይል ብቻ ቢቆም፥
ይሆንበታል ውድቀት።
፭፡ በዚህ መሠረት የሠራ
እርሱ ነው ጠቢብ ሰው፤
የለውም የሚያስፈራ፥
እስከ ፍጻሜውም።
፮፡ ልባችን መቅደስ እንዲሆን
ለልዑል እግዚአብሔር፤
ስለዚህ ቅዱስ መንፈሱን፥
አውርደው ለሰው።