መዝሙር 464 ዘምር በፍቅር በደስታ የዘፈን ግጥሞች
Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus. vertsion 2009
፩፡ ዘምር በፍቅር በደስታ
የወንጌሉን ቃል በሙሉ፤
የሱስ ይሰጣል ይቅርታ፥
ሕይወት ሰላምም ለሁሉ።
ዘምር ዘምር ወንጌሉን፥
ከሁሉ ያ ሀብት ይበልጣል።
ተካፈል በዕልልታ አሁን፥
ያንን ድንቅ የወንጌሉን ቃል።
፪፡ ዘምር የየሱስን ወንጌል
ፍርሃት ኀዘንም ይጠፋል፤
ራሱን የሠዋ በመስቀል፥
ሰውን ከመሞት ያድናል።
ዘምር ዘምር . . .።
፫፡ ዘምር የየሱስን ጥሪ
አውጀው በዓለም ዙሪያ፥
ዘምር ለጐበዝ ለፈሪ፥
መዳን ይገኛል ከዚያ።
ዘምር ዘምር . . .።
፬፡ ዘምር የየሱስን ክብር
ከርሱ የሚበልጥ የለንም፤
ዘምር የክርስቶስን ፍቅር፥
በሌላ ተስፋ አይገኝም።
ዘምር ዘምር . . .።