መዝሙር 433 ካለም መሄዴ ይደርሳል የዘፈን ግጥሞች
Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus. vertsion 2009
፩፡ ካለም መሄዴ ይደርሳል
እንዳሁንም አልዘምርም፤
ግን ወዳምላክ ቤት ስገባ፥
ደስታዬ እጅግ ይበዛል።
ፊት ለፊትም አየዋለሁ፥
የጸጋው ታሪክም ይህ ነው።
ፊት ለፊትም አየዋለሁ
በጸጋው ነው ያገኘሁት።
፪፡ ምድራዊ ቤቴ ይፈርሳል
ቀኑን ሳላውቀው ብቀርም፥
ይህንን ግን አውቀዋለሁ፥
ቦታ እንዳለኝ በሰማይ።
ፊት ለፊትም . . .።
፫፡ የፀሐይ ብርሃን ይጠፋል
ያሁን ምድቀቷ ይቀራል፥
ያን ጊዜ ጌታ ይለኛል
ታማኝ ልጄ አሁን ዕረፍ።
ፊት ለፊትም . . .።
፬፡ መብራቴን አብርቼ ቀኑን
መጠበቅ ብቻ አለብኝ።
መድኃኒቴ በሩን ሲከፍት፥
ነፍሴ ባምላኬ ታርፋለች።
ፊት ለፊትም . . .።