መዝሙር 394 ኀዘንተኛን የሚያጽናናው የዘፈን ግጥሞች
Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus. vertsion 2009
፩፡ ኀዘንተኛን የሚያጽናናው
የመድኃኒታችን ስም፤
ያን ቅዱስ ስም የሚጠራው፥
ይረዳል ይድናልም።
ቅዱስ ስም ብፁእ ስም፥
የዘላለም ተስፋ ነው።
ቅዱስ ስም ብፁእ ስም፥
የዘላለም ተስፋ ነው።
፪፡ ብርቱ ጋሻም ይሁንለት
ኃጢአት ሲፈትነው፤
ልመናውም ይፈጸምለት፥
ከየሱስ የለመነው።
ቅዱስ ስም . . .።
፫፡ ያ ክቡር የኢየሱስ ስም
ብፅዕናን ይሰጠናል፤
ሕይወት ደስታም ሰላምም፥
ከዚህ ስም አግኝተናል።
ቅዱስ ስም . . .።
፬፡ ወደ ሰማያዊ አገር
አድኖ ሲያደርሰን፤
ያን ቅዱስ ስም ላምላክ ክብር፥
እንዘምር ደስ ብሎን።
ቅዱስ ስም . . .።