መዝሙር 307 ሳዝን ስንገላታ የዘፈን ግጥሞች
Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus. vertsion 2009
፩፡ ሳዝን ስንገላታ
ጠላቴም ሲያጠቃኝ፥
ፈተና ሲከበኝ
ቀን ሲጨልምብኝ፤
የሱስ አንተ ብቻ ነህ
ልትረዳኝ የምትችል፥
እምነቴ ባንተ ነው
ሌላ አምባ የለኝም።
እረኛዬ እረኛዬ
እረኛዬ ከለላዬ፥
አንተ እኮ ነህ አለኝታ ጠባቂዬ።
ኢየሱስ ሆይ፥ ኢየሱስ ሆይ፥
ኢየሱስ ሆይ፥ መከታዬ፥
አንተ እኮ ነህ አለኝታ ጠባቂዬ።
፪፡ ስማኝ ጌታ የሱስ
ችግሬን ተመልከት፥
ልቤን አሳርፈው
ከኀዘን ከጭንቀት።
የእኔን ኃዘን አይተህ፥
ልብህ የሚራራ፥
ጌታ ሆይ አንተ ነህ፥
የእኔ ጽኑ ተስፋ።
እረኛዬ . . .።
፫፡ በስደት በችግር
በሚያስፈራው ሞገድ፥
በዓለም ጉዞዬ፥
በጨለማ መንገድ፤
ደግፈኝ ኢየሱስ፥
ከኔ ጋር ተራመድ፥
አላፊውን ደስታ፥
ልቦናዬ እንዳይወድ።
እረኛዬ . . .።
፬፡ ሥጋ ደካማ ነው
ሁሉንም ይመኛል፥
ስሜትም ክፉ ነው፥
ከውድቀት ያደርሳል።
ከዚህ ሁሉ ውድቀት፥
ጠብቀኝ ጌታዬ፥
እምነቴን አጽናልኝ፥
ሁነኝም መሪዬ።
እረኛዬ . . .።