መዝሙር 304 በኃጢአት ረግረግ ስኖር የዘፈን ግጥሞች
Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus. vertsion 2009
፩፡ በኃጢአት ረግረግ ስኖር ሰላምን አጥቼ
በጭንቀት ውስጥ ሰጥሜ ፍጹም ተስፋ አጥቼ
ሁሉን የሚችል አምላክ ጩኸቴን ሰማልኝ፥
ከሚያስጨንቀው አዘቅት ውስጥ አወጣኝ።
የኢየሱስ ፍቅር የኢየሱስ ፍቅር፥
ከ – ኃጢአት አንጽቶ አድኖኛል
የኢየሱስ ፍቅር የኢየሱስ ፍቅር፥
ከ – ኃጢአት አንጽቶ አድኖኛል
፪፡ በጭንቀት የሚረዳኝ ታማኙ ኢየሱስ ነው
ድንቅ በሆነው ምሕረቱ ብርታት የሚሰጠው
ችግርን የሚፈታ ፈጥኖ የሚደርሰው፥
ነፍስህን ለማዳን ነው ዛሬ እመነው።
የኢየሱስ ፍቅር . . .።
፫፡ ልቤን እሰጠዋለሁ እማጸነዋለሁ
በውስጤም ስለሚኖር እወድሰዋለሁ።
ልዘምር ላመስግነው ስለ ታላቅ ፍቅሩ፥
በታማኝነት ላገልግል በቤቱ።
የኢየሱስ ፍቅር . . .።