መዝሙር 291 እንደ የሱስ መድኃኒታችን የዘፈን ግጥሞች
Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus. vertsion 2009
፩፡ እንደ ኢየሱስ መንኃኒታችን፥
ወዳጅ የለም፤
ጌታ ሆኖ አብሮኝ ይኖራል፤
ግሩም ፍቅር።
በዓለም ውስጥ ያለው ሁሉ ሲያልፍ፥
ጌታ ግን ለዘላለም ይኖራል።
ልቤን አንጽቶ ሰላም ሰጥቶኛል፤
ግሩም ፍቅር።
፪፡ ኃጢአቴን ሁሉ ሊሰርይልኝ
የሱስ ሞተ፤
ለዘለዓለም ሕይወት ሊያወርሰኝ
እርሱ ሞተ።
የጠፋች ነፍሴን እርሱ ፈለጋት፥
ጸጋ ሊሰጣት ወደርሱ ጠራት።
ከዚያም በክብር ይጠብቃታል፤
ግሩም ፍቅር።
፫፡ እከተላለሁ የሚያፈቅረኝን
መድኃኒቴን፤
ሕይወቴን ሙሉ እሰጠዋለሁ
ለኢየሱስ።
በመተናኮል ሊያታልለኝ
ያ ክፉ ጠላቴ ቢመጣብኝ፥
ግን ጌታ ኢየሱስ ይጠብቀኛል።
ድል የኔ ነው።