መዝሙር 183 ያለ ደስታ ስኖር ሳለሁ የዘፈን ግጥሞች
Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus. vertsion 2009
፩፡ ያለ ደስታ ስኖር ሳለሁ
የሱስ ደምህ ፈሰሰልኝ።
ምሕረትን ልቀበል መጣሁ፥
የአምላክ በግ መጣሁ እርዳኝ።
፪፡ ከጨለማ ወደ ብርሃን
ጌታዬ ሆይ አውጣኝ እኔን።
ጊዜያቱ ሳያልፍብኝ፥
የአምላክ በግ ና አድነኝ።
፫፡ በምድር ተንገላትቼ
በችግርና በጭንቀት፥
እኖራለሁ ተዋርጄ፥
ጌታ ሆይ አውጣኝ ከጭንቀት።
፬፡ ቸሩ የሱስ ተቀበለኝ
ምሕረትህን አውርድልኝ።
በተስፋህ እንዳምን እርዳኝ፥
የአምላክ በግ መጣሁ መጣሁ።
፭፡ በመስቀል ሞት የገዛኸኝ
ጠላቴን አስወግድልኝ።
የአንተ ነኝ የአንተ ነኝ
እመጣለሁ ተቀበለኝ።