መዝሙር 175 የሱስ ሆይ ሕፃናትን የዘፈን ግጥሞች
Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus. vertsion 2009
፩፡ የሱስ ሆይ ሕፃናትን
ወዳንተ ስናቀርባቸው፥
አምነን ቅዱስ ተስፋህን
በስምህ ስናጠምቃቸው፥
በፍቅርህ ተቀበላቸው፥
በረከትህንም ስጣቸው።
፪፡ የሱስ ክርስቶስ ያንተ ደም
በአብ ፊት ይቀድሳቸው፥
መንፈስ ቅዱስ በቃልህ
በሕይወት መንገድ ይምራቸው።
ጽድቅን ይጐናጸፉ፥
መንግሥትህንም ይውረሱ።
፫፡ ታናናሾች በጎችህ
ከአንተ ዘንድ አይለዩ።
ሁልጊዜ በመንገድህ ሄደው፥
ካለው ሸር ይዳኑ።
ርስትህ እንዳይቀርባቸው፥
አንተ ራስህ ጠብቃቸው።