መዝሙር 163 ገስግሶ ሲያልፍ ቀናችን የዘፈን ግጥሞች
Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus. vertsion 2009
፩፡ ገስግሶ ሲያልፍ ቀናችን
ባምላክ ቃል ሠርክ እንጽና።
እርሱ ነው የሚያበራልን፥
በዚህ ዓለም ጨለማ።
ከጥንት ዘመን ጀምሮ፥
ኃይልን ደስታን ሰጥቶ።
ወደ ሰማይ በሚመራ፥
በዚህ ቃል ዘወትር እንጽና።
፪፡ በዚህ ዓለም ስንዋትት
እንደ ጥንቱ ቅዱሳን።
ቅዱስ ቃሉን ለማዳመጥ፥
እንሰብሰብ ሲጠራን።
አባት ከልጆቹ ጋር፥
ያቅርብለት ምስጋና።
በምሕረቱ እንዲያየን፥
ዘወትር ተግተን እንለምን።
፫፡ ባርከነ ጠብቀነ
ጸጋን ሞገስን ስጠን።
ዘወትር በምክርህ ምራነ፥
በመንገድ ብርሃን ሁነን።
መልስልን ፊትህን፥
ሰላምህን አካፍለን።
ሥሉስ አምላክ ስለ ፍቅሩ፥
ይመስገን በዓለም ሁሉ።