መዝሙር 136 አምላኬ ሆይ-በጸሎቴ አንተን እማጠናለሁኝ የዘፈን ግጥሞች
Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus. vertsion 2009
፩፡ አምላኬ ሆይ – በጸሎቴ አንተን እማጠናለሁኝ
በዘላለማዊ ፍቅርህ – እኔን ኃጥእ ይቅር በለኝ።
ስለ ታላቁ ምሕረትህ – በደሌን አስወግድልኝ
ፊትህን አትሰውርብኝ – ማረኝ እንደ ቸርነትህ።
፪፡ አጥፍቻለሁ አውቀዋለሁ – በፊትህ እናዘዛለሁ
ብትቀጣኝ ይገባኛል – በአንተ ፊት አጥፍቻለሁ።
ፈቃድህን ተላልፌ – ወንድሜንም በድያለሁ
አምላኬን አሳዝኛለሁ – ትእዛዛትህን አፍርሻለሁ
፫፡ በዓመፃ ተጸንሼ – በኃጢአት ተወለድሁኝ
መላ ዘመኔ በድዬ – መንፈስህን አሳዘንሁኝ።
በይቅርታህ ተመልከተኝ – በሂሶጵ ረጭተህ አንጻኝ
ልክ እንደ በረዶ አጥራኝ – ከፍርድ ኵነኔ አድነኝ።
፬፡ ብታደቀኝ ብትሰብረኝ – እንደገና ደስ አሰኘኝ
የደስታ ሐሤት አሰማኝ – ንጹህ ልብን ፍጠርልኝ
ባንተ ታምኜ እንድኖር – የጽናት መንፍስህን ስጠኝ፥
በጸጋህ ሙላት አድነኝ – ደስታህንም መልስልኝ።
፭፡ በንስሐ ቀርቤአለሁ – ልቤን መሥዋዕት እሰጣለሁ
ማዳንህን አይቻለሁ – ለመመስከር ቆርጫለሁ።
ጥፋቴን ሁሉ ደምስሰህ – በፍቅርህ ልጅህ ሁኛለሁ፥
ዘወትር አመሰግናለሁ – በፊትህም እሰግዳለሁ።