መዝሙር 130 የሱስ ኃጢአቴን ወስዶ የዘፈን ግጥሞች
Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus. vertsion 2009
፩፡ የሱስ ኃጢአቴን ወስዶ
በመስቀል ላይ ሞተልኝ።
ከፍርድም ከኩነኔም
አርነት አወጣኝ።
ለየሱስ ጭንቄን ሁሉ
አሁን አስታውቃለሁ።
በክቡር ደሙ ብቻ
ኃጢአቴን ያጠፋል።
፪፡ ችግሬን ሁሉ ለእርሱ
አሁን እነግረዋለሁ።
በታላቅ ቸርነቱ
ረድኤት ይሆነኛል።
ከችግርና ድካም
ዕረፍትን ይሰጠኛል
እርሱም በጥልቅ ኀዘኔ
ጽናት ይሆነኛል።
፫፡ ተስፋዬንም በየሱስ
ፍጹም አድርጌአለሁ።
በቀኝ እጁ ሲይዘኝ
አንዳችም አልፈራም
ያ ድንቅ ስም የሱስ ክርስቶስ
ልዑል አማኑኤል።
ለነፍሴ መጽናናት
ሲሆን ይበቃኛል።
፬፡ እኔ የሱስን ልምሰል
በትሕትና ገርነት።
እንደ የሱስም ልሁን
በሕይወቴ ሁሉ።
ዕለተ ሞቴ ሲደርስ
ወደ አእላፋት
ብፁዓን እሄዳለሁ
ልኖር በአንድነት።