መዝሙር 128 ከበደሌ ከኃጢአቴ የዘፈን ግጥሞች
Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus. vertsion 2009
፩፡ ከበደሌ ከኃጢአቴ
ወዴት ልሽሽ ኦ አምላኬ?
በጣም እጨነቃለሁ
ሕግህን ሁሉ አፍርሼ
ከአንተ ርቄ ሸሽቼ
ፍርድህን እፈራለሁ።
ነፍሴንም ኀዘን ደቆሰው
ልቤንም ጸጸት ሰበረው።
ጌታዬ ሆይ ራራልኝ
ምሕረት አድርግልኝ።
፪፡ አምላክ ሆይ ቃልህ ሕይወት ነው፤
ለነፍሴ በጣም ጣፋጭ ነው፤
ልቀበለው እሻለሁ።
የሱስ ወዳለም መጥቶአል፤
ኃጢአቴን ደምስሶልኛል፤
እኔ በርሱ ድኛለሁ።
ወንበዴውን የተቀበለው፥
በገነትም ያሳረፈው፥
እኔን እንደሚቀበል፥
ቅዱስ ወንጌል ነግሮኛል።
፫፡ የሱስ ክርስቶስ የዳዊት ልጅ፥
ልቤን ከእጆቼ ጋራ
ወዳንተ አነሣለሁ።
እኔን የረከስሁ አጥራኝ፤
ከኃጢአት እድፍ አንጻኝ፤
በአንተ አምናለሁ።
እንደ ጠፋው በግ ነበርሁኝ፥
በአንተ ግን ተገኘሁኝ፤
አንተ የምትራራ
አኑረኝ ካንተ ጋራ።