መዝሙር 113 የምድር አሕዛብ ሁሉ የዘፈን ግጥሞች
Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus. vertsion 2009
፩፡ የምድር አሕዛብ ሁሉ
ለእግዚአብሔር ዘምሩ።
ለእርሱም በደስታ ተገዙ
በፊቱም በእልልታ ግቡ።
፪፡ እርሱ አምላክ ነው እወቁ
ፈጣሪያችንም ነው እርሱ።
ስለዚህ እኛ የእርሱ ነን፥
የመሰማሪያውም መንጋ ነን፡
፫፡ ወደ ደጆቹ ስንገባ
ወደ ቤቱም በምስጋና።
ስሙን ሁላችሁ ባርኩ
በመልካም ዜማም ወድሱ።
፬፡ እግዚአብሔር ቸር ነውና
ቸርነቱም ለዘላለም።
እውነቱም ለል-ጅ ልጅ ነው
ቃሉም ዘለዓለም ሕያው ነው።