መዝሙር 104 አምላክ ይመስገን የዘፈን ግጥሞች
Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus. vertsion 2009
፩፡ አምላክ ይመስገን
ስለ ታላቅ ጸጋው
በግሩም ርኅራኄው፥
ልጆቹን ያስባል።
ወድሱት እናንተ
የሰማይ ሠራዊት፥
ስለ ምሕረቱ።
፪፡ ልጁም ይመስገን
ግሩም ነው ቸርነቱ።
በምሕረቱ
ለሕዝቡ ይራራል።
እናንተ በዓለም፥
የምትኖሩ ሁሉ፥
እርሱን ወድሱት።
፫፡ ለመንፈስ ቅዱስ
ምስጋና እናቅርብ፥
ከአብ ከወልድም
ተልኮአል ወደኛ።
አብን ወድሱት
ወልድን መንፈስንም
አሁን ወድሱ።